image
image
image
image
image

በልደታ ክፍለ ከተማ የወረዳ 08 አስተዳደር "ኑ ተስፋን እንትከል" በሚል መሪ ቃል የመንግስት ሰራተኞች በጊዶ ዋሻ ችግኝ ተክለዋል።

ሀምሌ 10, 2018
በእለቱም ተገኝተዉ ንግግር ያደረጉት የወረዳ 08 ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ደረጄ ፈይሳ ከክረምት በጎ ፍቃድ አንዱ የሆነዉ የችግኝ ተከላ ነዉ ችግኝ በመትከል ሁሉም አካላት አሻራ በማስቀመጥ የአረንጓዴን ልምላሜን በማሳደግ የሀገራችንን የአየር ንብረት ተስማሚ ማድረግ አለብን ብሏል። የወረዳ 08 ብልግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኢንጅነር ይትባረክ ብርሃነ በበኩላቸው ችግኝ መትከል ብቻ ሳይሆን መንከባከብም አለብን የምንተክላቸዉን ችግኞች በጥንቃቄ በመትከል አሻራችንን ማሳረፍ አለብን ሲሉ ተናግረዋል።

መልዕክትዎን ይላኩ